bankofabyssinia.com

Category: News

ባንካችን አቢሲንያ ከፋስትፔይ ጋር ዲጂታል የሐዋላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ
Post

ባንካችን አቢሲንያ ከፋስትፔይ ጋር ዲጂታል የሐዋላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ

አቢሲንያ ባንክ ዛሬ ነሐሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከፋስትፔይ (Fastpay LLC) ጋር ዓለም ዓቀፍ ዲጂታል የሐዋላ አገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ የሚረዳውን የሳይበር ሶርስ (Cybersource) የክፍያ አማራጭ ቴክኖሎጂ የስትራቴጂክ አጋርነት ስምምነት በሃያት ሬጀንሲ ሆቴል ተፈራርሟል፡፡  ባንካችንን በመወከል የደንበኞች ማኔጅመነት ዋና አፊሰር አቶ ደሳለኝ ይዘንጋውና በፋስትፔይ በኩል ደግሞ  የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍጹም መርዳሳ የመግባቢያ ስምምነቱን ፈርመዋል፡፡...

ባንካችን አቢሲንያ በፈጠራ ልህቀት የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት
Post

ባንካችን አቢሲንያ በፈጠራ ልህቀት የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት

አቢሲንያ ባንክ በቅርቡ በተካሄደው 23 ኛው ኮኔክትድ ባንኪንግ ስብሰባ (23rd Edition of Connected Banking Summit – Innovation and Excellence Awards Ethiopia!) ላይ የፈጠራ ልህቀት ተሸላሚ ሆኗል።ይህንንም የፈጠራ ልህቀት (𝐄𝐱𝐜𝐞𝐥𝐥𝐞𝐧𝐜𝐞 𝐢𝐧 𝐈𝐧𝐧𝐨𝐯𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧) ሽልማት የአክሴፕታንስ ኔትዎርክ ዳይሬክተር አቶ ተዎድሮስ አባይ ነሃሴ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተካሄደ ዝግጅት ላይ ባንኩን ወክለው ተቀብለዋል።ይህ ሽልማት ባንካችን የደንበኞች ተሞክሮን...

ባንካችን አቢሲንያ በሐምሌ ወር የውጭ ምንዛሬ ጥያቄ ላቀረቡ ደንበኞቹ 94 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አቀረበ!
Post

ባንካችን አቢሲንያ በሐምሌ ወር የውጭ ምንዛሬ ጥያቄ ላቀረቡ ደንበኞቹ 94 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር አቀረበ!

አቢሲንያ ባንክ የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ብሎም በኢኮኖሚው የዋጋ መረጋጋት አንዲኖርና የደንበኞችን የገቢ ንግድ ለመደገፍ የበኩሉን አስተዋፆ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ በተለይም ለምግብ፣ እንዲሁም ለሌሎች ወደ ሀገራችን ለሚገቡ ስልታዊ ሸቀጦች (Strategic Commodities) ቅድሚያ በመስጠት ለደንበኞቹ በተለያየ መጠን የውጭ ምንዛሬ ሲያቀርብ ቆይቷል።በሐምሌ ወርም ባንካችን ከደንበኞቹ ለቀረቡት በርካታ የውጭ ምንዛሬ ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ጥያቄዎቹን ያስተናገደ...

ማሳሰቢያ፤ ለተከበራችሁ ስማችሁ ከዚህ በታች ለተዘረዘረው የባንካችን ደንበኞች
Post

ማሳሰቢያ፤ ለተከበራችሁ ስማችሁ ከዚህ በታች ለተዘረዘረው የባንካችን ደንበኞች

ለተከበራችሁ ስማችሁ ከዚህ በታች ለተዘረዘረው የባንካችን ደንበኞች፣ ሂሳቦቻችሁ ለ15 ዓመትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ሳይንቀሳቀሱ በመቆየታቸው የእነዚህ ሂሳቦች ባለቤቶች ወይም ህጋዊ ባለመብቶች ነን የምትሉ ደንበኞች እስከ ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ሂሳቦቹ በሚገኙባቸው ቅርንጫፎች ወይም በዋናው መ/ ቤት ህጋዊ ማስረጃችሁን በማቅረብ ክፍያዎቹን መጠየቅ ወይም ሂሳቦቹን ማንቀሳቀስ የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

ባንካችን አቢሲንያ በሁሉም ቅርንጫፎቹ ወረቀት አልባ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
Post

ባንካችን አቢሲንያ በሁሉም ቅርንጫፎቹ ወረቀት አልባ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

ባንካችን አቢሲንያ በዛሬው ዕለት በአዲስ መልክ በተዋቀረው የባንካችን ራስ ልዩ ቅርንጫፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ፣ የባንካችን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ የበላይ የሥራ አመራሮችና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የወረቀት አልባ የባንክ አገልግሎቱን በይፋ አስመርቆ ስራ አስጀምሯል።ይህ አዲስ አሠራር ገንዘብ ማስተላለፍ፣ ጥሬ ገንዘብ ማስገባትና ማውጣት፣ ሒሳብ መክፈትና ሌሎች በቅርንጫፍ በኩል...

ባንካችን አቢሲንያ የ2024/25 የበጀት ዓመት የሥራ አመራር ጉባዔውን አካሄደ
Post

ባንካችን አቢሲንያ የ2024/25 የበጀት ዓመት የሥራ አመራር ጉባዔውን አካሄደ

አቢሲንያ ባንክ የተጠናቀቀውን የ2024/25 በጀት ዓመት የሥራ አመራር ጉባዔውን ሐምሌ 17 እና 18 ቀን 2017 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ሲያካሂድ ቆይቶ ሊበረታቱና ሊሻሻሉ የሚገባቸውን የሥራ አፈፃፀሞች በመለየትና የባንኩን ቀጣይ ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች በማስቀመጥ በስኬት ተጠናቅቋል። በስብሰባው ላይ በዋና ዋና ቁልፍ መለኪያዎች አፈፃፀም ከዕቅድ አንፃር የተሠሩ ሥራዎች በዲስትሪክቶች በሰፊው የተነሱ ሲሆን አፈጻፀማቸው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንፃር...

ሥነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት
Post

ሥነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት

ሥነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት ለባንካችን ከፍተኛ አመራሮች ‘‘ሥነ ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት’’ በሚል ርዕስ ጥር 30 እና የካቲት 1/ 2017 ዓ.ም በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ስልጠና ተሰጠ፡፡ በስልጠናው የተገኙት የባንካችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ በቃሉ ዘለቀ ስልጠናውን አብረን በመውሰድ ወደ ተግባር መለወጥ ይገባል ብለዋል። ይህ ‹‹ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት!›› በሚል ርዕስ ለሁለት...

ባንካችን አቢሲንያ የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ
Post

ባንካችን አቢሲንያ የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ

የአቢሲንያ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ እና የስራ አመራር አባላት ባለፉት ስድስት ወራት በባንኩ በተሰሩ ዋና ዋና ክንውኖች ላይ ጥር 23 እና 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሐይሌ ግራንድ ሆቴል በጋራ ግምገማ አካሂደዋል፡፡ በግምገማው ወቅት ከእቅድ አንፃር በዋና ዋና መለኪያዎች ረገድ የተሰሩ ስራዎች በዲስትሪክት ፅ/ቤቶች ተነስተው ሰፊ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን የባንካችን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ በቃሉ ዘለቀ በአፈጻጸማቸው...

ባንካችን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ የሚሰጠውን ማዕከል በድምቀት አስመረቀ
Post

ባንካችን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ የሚሰጠውን ማዕከል በድምቀት አስመረቀ

ባንካችን አቢሲንያ በዋናው መስሪያ ቤት በሚገኘውና ከጫካ ቡና ጋር በመተባበር የከፈተውን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በካፌ የሚሰጠውን ማዕከል በትላንትናው ዕለት ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም የባንካችን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ የጫካ ቡና ባለቤት አቶ ብስራት በላይ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል፡፡ አቢሲንያ ባንክ ሁሌም ቢሆን ዘመናዊ የሆኑ የባንክ አገልግሎቶችን በማቅረብ...

Call Now Button